ትምህርት ፅ/ቤት

Lorem ipsum dolor sit amet, consectetur adipiscing elit. Ut elit tellus, luctus nec ullamcorper mattis, pulvinar dapibus leo.

ራዕይ

በአቃቂ ቃሊት ከ/ከተማ ት/ጽ/ቤት ውጤታማ የትምህርት ስርዓት በማስፈን በ2020 ዓ.ም ዓለም አቀፋዊ ተወዳዳሪ የትምህርት ተቋማትንና በልማት፣ በድሞክራሲና በመልካም አስተዳደር ግንባታ ቁልፍ ሚና የሚጫወቱ የተሟላ ስብዕና ያለው የትምህርት ተቋማትን ማፍራት፡፡

እሴቶች

  • ለትምህርት ጥራት ቅድሚያ እንሰጣለን
  • በመልካም ሥነምግባር የታነፁ ዜጎችን እናፈራለን
  • ፈጠራና ችግር ፈቺነትን እናበረታታለን
  • ጥናትና ምርምር መለያችን ነው
  • በእውቀትና በእምነት እንመራለን
  • ግልፅነት
  • ተጠያቂነት
  • ለለውጥ ዝግጁ ነን
  • የላቀ አገልግሎት እንሰጣለን
  • በጋራ መስራት መገለጫችን ነው

ተልዕኮ

   በአቃቂ ቃሊት ክፍለ ከተማ ት/ፅ/ቤት በት/ት ስራ ላይ በባለቤትነት በመሳተፍ ለት/ት መዋቀሩ አካላትና በት/ት መስክ ለተሰማሩ ባለድርሻ አካላት ሙያዊና ቴክንካዊ ድጋፍ በመስጠት ፣ ስራዎች፣ በተቀመጠላቸው የጊዜ ሰሌዳ ተግባራዊ እንዲሆን መከታተልና መደገፍ፤ አጋር ድርጅቶችን በማስተባበር ት/ት ተቋማትን በፍትሃዊነት በማስፋፋት ደረጃውን የጠበቀና በቴኮኖሎጂ የተደገፋ ት/ት በተስማሚ ፕሮግራሞች ለህ/ሰቡ እንዲደርስ የበኩሉን ድጋፍ ማድረግ፡፡

 

 

 

ጽ/ቤቱ የሚገኝበት  አድራሻ  7ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 702

ጽ/ቤቱ ግዴታ

  • የአገልግሎት ለመስጠት የሚያስፈልጉ ግብዓቶች አሟልቶ መገኘት ፤
  • ስለአገልግሎቱ የተሟላ መረጃ መስጠት፤
  • አገልግሎቶቹን በተቀመጠው ስታንዳርድ መሰረት መስጠት ፤
  • ለተገልጋዩ ህብረተሰብ ሙያዊ የምክር አገልግሎት የመስጠት፤
  • ለተገልጋዩ ህብረተሰብ ለሚፈጠሩ ቅሬታዎች ቀልጣፋ ምላሽ መስጠት፤
  • ለተገልጋዩ ፍትሃዊ አገልግሎት መስጠት፤
  • በየጊዜው የህብረተሰቡ እርካታ ያለበት ደረጃን በዳሰሳ ጥናት በመለካት የህብረተሰቡን እርካታ ማወቅ
  • የትምህርት ተቋማትን ከአዋኪ ነገሮች ነጻ ማድረግ

የተገልጋዮች መብት

  • ስለ አገልግሎቱ የተሟላ መረጃ መግኘት
  • የምክር አገልግሎት ማግኘት
  • ቅሬታ የሚያቀርብበት ግልጽስርዓት፣ለሚያርቡት ቅሬታ በቃል ሆነ በጽሁፍም ፈጣን ምላሽ ማግኘት
  • በየሶስት ወሩ የተቋሙ የእቅድ አፈጻጸም ግምገማ ላይ መሳተፍ
  • በየደረጃው የሚገኙ የትምህርት ሴክተሩ ተቋማት በየሚያካሂዱት የምዛና የዕውቅና ስርዓቶች ላይ በተደራጀ መልኩ መሳተፍ
  • ጥራቱንና ተገቢነቱን የተረጋገጠ ትምህርት በፍትሃዊነት የማግኘት መብት

የተገልጋይ ግዴታዎች

  • ትክክለኛ መረጃዎችን በማቅረብ
  • የአገልግሎት ቅድመ ሁኔታዎችን መሟላት ማቅረብ
  • የአገልሎት ሰጪ ተቋማትን ህግና ስርዓትን ማክበር
  • በክትትልና ሱፐርቪዝን የሚሰጡ የማሻሻያ ግብዓቶችን ተግባራዊ ማድረግ
  • ወላጆችን ህብረተሰቡ የትምህርት ስርዓቱን በግብዓትና በመማር ማስተማር ሂደት እና ውጤት ማሻሻል ድርሻውን መወጣት
  • የትምህርት ተቋማትን ከሰው ሰራሽ አዋኪ ነገሮች መጠበቅ
  • ወላጆችና ህበረተሰቡ ተማሪዎችን መምከር
  • ተገላጋዩ የሚጠበቅበትን ዲፕሊን ማክበር

የቅሬታ አቀራረብና አፈታት ሥርዓት

  • ቅሬታ ያጋጠመው ዜጋ ቅሬታውን በቀጥታ አገልግሎት ለሰጠ በቃል፣በጽሁፍ፣በስልክ መግለጽ ይችላል፤
  • ቅሬታ የቀረበበት ፈጻሚም የቀረበለትን ቅሬታ አጣርቶ ወዲያውኑ ለቅሬታ አቅራቢው ተገልጋይ ተገቢውን ምላሽ መስጠት አለበት፤
  • በተሰጠው ምላሽ ያልረካ ተገልጋይ ቀጥሎ ላለው  የቅርብ ሃላፊ አገልግሎት  ላላገኘበት  የስራ ሂደት /ቅሬታው እንዲፈታለት  ማቅረብ ይችላል፤
  • ደረጃውን ጠብቆ የቀረበለት የቡድን/ስራ ሂደቱ ሃላፊ/አገልግሎት ላላገኘበት የስራ ሂደት /ቅሬታውን  አጣርቶ ወዲያውኑ ምላሽ መስጠት አለበት፤
  • በተሰጠው ምላሽ ያልረካ ተገልጋይ ለተቋሙ የቅሬታና አቤቱታ ሰሚ አካል ወዲያውኑ ቅሬታውን ያቀርባል፤
  • የቅሬታና አቤቱታ ሰሚ አካል የቀረበለትን አቤቱታ አጣርቶ ምላሽ መስጠት በሚችልባቸው  ጉዳዮች ላይ በ5 ቀናት ውስጥ ምላሽ ይሰጣል፤
  • የቅሬታና አቤቱታ ሰሚ አካል የቀረበለትን አቤቱታ በማጣራት የበላይ አመራር ውሳኔ  የሚያስፈልገው ከሆነ ከውሳኔ ሃሳብ ጋር ያቀርባል፤
  • የመ/ቤቱ የበላይ አመራር ከሚቀርቡለት የውሳኔ ሃሳቦች ላይ በመነሳት በሶስት  ተከታታይ  የስራ ቀናት  ውስጥ  የመጨረሻ  ውሳኔ ምላሽ ይሰጣል፤
  • በዚህም ውሳኔ ተገልጋዩ ዜጋ ካልረካ በየደረጃው /በክፍለከተማና በአዲስ አበበ ከተማ አስተዳዳር/ለሚገኘው የህዝብና ቅሬታ ና አቤቱታ ሰሚ ዋና የስራ ሂደት ቅሬታውን ያቀርባል፡፡
  • በዚህም ውሳኔ ተገልጋዩ ዜጋ ካልረካ ለሚመለከተው  ፍርድ ቤት፣ጸረ ሙስና ኮሚሽን፣ለህዝብ እንባጠባቂ ፣ለሰብዓዊ መብት ኮሚሽን መብት ማቅረብ ይችላል፡፡