አቃቂ ቃሊቲ ትራንስፖርት ቅርንጫፍ ጽ/ቤት

በጽ/ቤቱ ስር 5 የሥራ ክፍሎች ይገኛሉ

  1. የጽ/ቤት ሀላፊ
  2. የኦኘሬሽክ ክፍል ዳይሬክተር
  3. የህዝብ ጭነት ስምሪት ቁጥጥር ድልድል ቡድን መሪ
  4. የመሰረተ ልማት ክትትል ቁጥጥር ቡድን መሪ
  5. የንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ቡድን መሪ

ራዕይ

ተደራሽ ፣ ቀልጣፋ፣ አስተማማኝ ፣ ምቹ፣ የተጠበቀ እና ከአካባቢ ጋር ተስማሚ የሆነ አቅምን ያገናዘበ የብዙሀንና የጭነት ትራንስፖርት ለህብረተሰቡ ማቅረብ

ተልዕኮ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንፖርት ቢሮ የህዝብና ጭነት ትራስፖርት አገልግሎት ዘርፍ የሚሰሩ ማህበራትና ተቋማትን ፣ ግለሰቦችን በማደራጀት የትራንስፖርት መሰረተ ልማቶችን በማልማትና በማስተዳደር ጥናቶችን በማካኤድ ስምሪት በመስጠት በመቆጣጠር እና መረጃን ተደራሽ በማድረግ የተገልጋይ ህብረተሰብ የተቀናጀ የትራንስፖርት አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆን ማድረግ፡፡

እሴት

  • ለለውጥ ዝግጁነት 
  • ፍትሀዊነት 
  • ተጠያቂነት
  • ግልፅነትና
  • የላቀ አገልግሎት 

የሚሰጡ አገልግሎቶች

  1. አዲስ ታፔላ መስጠት ማደስ
  2. የሀይገርና ታክሲ ስምሪት ማፅደቅ መከታተል
  3. የመጠበቂያ መጠለያዎችን የመቆጣጠር የመከታተል ስራ
  4. ተራ አስከባሪዎችን የመቆጣጠር የመከታተል ስራ

በቅርንጫፍ ጽ/ቤት ደረጃ የሚሰጥ አገልግሎት

ተ.ቁ

የሚሰጡ አገልግሎቶች ዓይነት

አገልግሎቱ የሚሰጥበት ቦታ

የአገልግሎት ስታንዳርድ/ደረጃ

የሚሰጥበት ሁኔታ

ከተገልጋይ የሚጠበቅ ቅድመ ሁኔታዎች

ጊዜ /በሰዓት/

ጥራት

/በ%/

1

የህዝብ ትራንስፖርት ስምሪት ድልድል   አገልግሎት መስጠት፣

1.1

የታክሲ ማህበራት የስምሪት ድልድል ማጽደቅ

የትራንስፖርት ኦፕሬሽን ዳይሬክቶሬት

0፡16

100

በአካል

§  የስምሪት መስመር ሽክርክሪት በተቀመጠው አሰራር መሰረት አዘጋጅቶ ማቅረብ፤

1.2

የድጋፍ ሰጭ የስምሪት መስመር አገልግሎት መስጠት

0፡30

100

በአካል

§  የተዘጋጀለትን ፎርም ሞልቶ ማቅረብ፤ 

§  አዲሰ ከሆነ ሊብሬና መታወቂያ፤  ባለቤት ካለሆነ ህጋዊ ውክልና ነባር ከሆነ የቀድሞ የታፔላ መመለስ፤

§  የአገልግሎት ክፍያ  590 ብር መፈጸም

1.3

የስምሪት መስመር አገልግሎት ውል ማቋረጥ

0:30

100

በአካል

§  በባለበቱ ወይም ህጋዊ ውክልና ዯለው አካል በአካል መቅረብ አለበት

§  የታደሰ መታወቂያ

§  የውስጥ እና የውጭ ታፔላ ይዞ መገኘት አለበት

1.4

የማህበራት የተማሪዎች ሰርቪስ አገልግሎት ጥያቄ ማስተናገድ

0፡20

100

በአካል

§  የተሽከርካሪዎችን ድልድል በተቀመጠው አሰራር መሰረት አዘጋጅቶ ማቅረብ፤

2.

የሕዝብ ትራንስፖርት ስምሪት ክትተልና ቁጥጥር ማካሄድ

2.1

የአሽከርካሪዎች ቅጣት ክፍያ፤

የትራንስፖርት ኦፕሬሽን ዳይሬክቶሬት

0፡10

100

በአካል

§  በትራንስፖርት ስምሪት ቁጥጥር ሠራተኛ የተቆረጠ የቅጣት ማዘዣ /ደረሰኝ/፤

3

ጭነት የትራንስፖርት አገልግሎቶች የኦፐሬሽን ስርዓትና መቆጣጠር

3.1

የአሽከርካሪዎች ቅጣት ክፍያ፤

የትራንስፖርት ኦፕሬሽን ዳይሬክቶሬት

0፡10

100

በአካል

§  በትራንስፖርት ስምሪት ቁጥጥር ሠራተኛ የተቆረጠ የቅጣት ማዘዣ /ደረሰኝ/፤

  • ከተገልጋይ የሚጠበቅ

አዲስ የኮድ 3 እና ቅጥቅይ ተሽከርካሪዎች ታፔላ ለመውሰድ ሲመጡ የሚያስፈልጉ

  1. ኦርጅናል ሊብሬ አድራሻው አቃቂ ቃሊቲ መሆን ይኖርበታል
  2. ሶስተኛ ወገን
  3. ቦሎ
  4. ንግድ ፈቃድ
  5. የቀበሌ መታወቂያ
  6. ህጋዊ ውክልና ወይም ባለቤት መሆን ይኖርበታል

አድራሻችን፡-ማሰልጠኛ ቅጥር ግቢ ውስጥ በር ሁለት

Email;Akakikalitytrabranch@gmail.com